top of page

David Weinstein – በአማርኛ

ስሜ ዳዊት ዊንስተን እባላለሁ፡

በካምብሪጅ የህዝብ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ሁለት ልጆች ስላሉኝ ኩራት ይሰማኛል፣ አንዱ 6ኛ ክፍልና ሌላኛው 11ኛ ክፍል ናችው። ትምህርት ቤቶቻችን ከኛ ቁርጠኛና ጎበዝ አስተማሪዎች፣ሰራተኞች፣ቤተሰቦችና አጋሮች

 ከማህበረሰብ ድርጅቶችና የከተማ ፕሮግራሞች ስፍር ቁጥር የሌላቸው ሀብቶች አሏቸው። ጥንካሬያችን እንዳለ ሆኖ፣ ሁሉም ልጆቻችን እንዲበለፅጉ የሚያስፈልጋቸውን መሳሪያ እና ድጋፍ እንዲያገኙ የዘር፣ የፆታ እና የኢኮኖሚ እድል ክፍተቶችን ለመዝጋትና ፀረ-ዘረኝነትና የዘር እኩልነትን በሁሉም የካምብሪጅ ክፍል ውስጥ ለማስፈን አሁንም ስራ ይቀረናል።

 

በትምህርት ቤት ኮሚቴ ውስጥ በነበርኩበት ጊዜ፣ በዘመቻዎቼ ውስጥ በተከታታይ ለገለጽኳቸው ትልልቅ ግቦች ትርጉም ያለው እድገት አድርገናል። ለድጋሚ ለመመረጥ እየተወዳደርኩ ያለሁት ገና ስራ ስላልጨረስን ነው፡ እነዚህ የረጅም ጊዜ ፕሮጀክቶች እንደመሆናቸው እነሱን ለመተግበር  ጠንካራ አመራርና ቀጣይ ቁርጠኝነትን ይጠይቃል።

 

እንደ ወላጅ፣ የቀድሞ የመንግስት ትምህርት ቤት መምህር እና የትምህርት ምሁር፣ አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ከብዙ አቅጣጫ ልምድ አለኝ። በድጋሚ ከተመረጥኩ፣ ከካምብሪጅ ቤተሰቦች ጋር መገናኘቴን ለመቀጠል እና ልምዴን ተጠቅሜ ለሁሉም ልጆቻችን እድሎችን ለመጨመር ቃል እገባለሁ።

 

እ.ኤ.አ. በኖቬምበር 7፣ 2023 #1 ድምጽዎን እጠይቃለሁ። ከእርስዎ ጋር ለመስራት በጉጉት እጠባበቃለሁ!

 

የሚከተሉት ነጥቦች እኔ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ነገሮች፡

  • በትምህርት ቤቶቻችን ያለውን የዘር፣ የፆታ እና የኢኮኖሚ እድል ክፍተቶችንመዝጋት።

  • ለሁሉም የካምብሪጅ ልጆች እና ቤተሰቦች ከማህበረሰብ ተሟጋቾች፣ ከከተማዋ፣ ከድርጅታዊ አጋሮች እና ከንግዶች ጋር በመተባበር የተቀናጀ የሙያ ስነ-ምህዳርን መገንባት።

  • የእያንዳንዱን ልጅ ፍላጎቶች መለየታቸውንና መሟላታቸውን የሚያረጋግጡ “የተማሪ ስኬት እቅዶችን” ያቋቁሙ፣ እና ሁሉም ለማደግ እና የላቀ ውጤት ለማግኘት ይበረታታሉ። ማንም ሰው  የአቅሙን ለመድረስ ድጋፍ ማጣት የለበትም።

  • የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶቻችንን (ከ6-8ኛ ክፍል) በአስተማሪ ትብብር፣ በተሻሻለ የትምህርት እድል፣ ለማህበራዊ ሰራተኞች እና ለቤተሰብ ግንኙነቶች ድጋፍ፣ እና ተጨማሪ ስነ ጥበባት፣ ስፖርት እና ተጨማሪ ትምህርት ማበርከት።

  • ሁሉም ቤተሰቦች እና ተንከባካቢዎች በት/ቤታችን ውስጥ ሙሉ አቅም ያላቸው ተሳታፊዎች እንዲሆኑ ተግባቦትን እና ግልፅነትን ማሻሽል።

  • ምርጥ መምህራንን በመቅጠር፣ በመደገፍ እና በማቆየት 30% የቀለም መምህራንን መቅጠር።

bottom of page